የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል በግንቦት ሰባት ስም ከሚደረጉት ስልጠናዎች የመጨረሻው ምርቃት አካሄደ
ጥቅምት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ለ 90 ቀናት በተከታታይ በወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ እና የመረጃ እና ደህንነት ትምህርቶች ያሰለጠናቸውን ታጋዮች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተለያዩ የተቃዋሚ ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ባስመረቀበት ወቅት...
View Articleሰማያዊ ፓርቲ በብሄራዊ ደረጃ ለሚደረገው ትግል ህዝቡ ተባባሪ እንዲሆን ጠየቀ
ጥቅምት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ የሀገራችን አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሱና እየከፉ የመምጣታቸውን ያህል ገዢው ፓርቲ ቆም ብሎ ከማሰብ ይልቅ ወደ ማይወጣው አዘቅት ውስጥ ሀገሪቷን ጭምር እያንደረደራት ይገኛል ብሎአል። ኢህአዲግከዲሞክራሲያዊ...
View Articleሚኒስትሮች ባልተወራረደ የመንግስት ገንዘብ ጉዳይ ላይ ጎራ ለይተው ተከራከሩ
ጥቅምት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ዋና ኦዲተር፣ አባካኝ የመንግስት ተቋማት በሚል ለጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት እና ለተወካዮች ም/ክር ቤት አፈ ጉባኤ ያቀረበው ሪፖርት ለህዝብ ይፋ ይሁን አይሁን የሚለው ጉዳይ ሚኒስትሮችን አወዛግቧል። አቶ አባዱላ ገመዳ፣ አቶ ደመቀ መኮንን፣ አቶ አዲሱ...
View Articleበደቡብ ሱዳን ጦርነት እንደገና አገረሸ
ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሪክ ማቻር የሚመራው የተቃዋሚ ቡድን ቤንቲዩና ሮቡክና የተባሉ ቦታዎችን መቆጣጠሩን መረጃዎች አመለክተዋል። ሁለቱን ተፋላሚ ሃይሎች ለማስታረቅ በኢትዮጵያ በኩል ሲደረግ የነበረው ድርድር ውጤት አለማምጣቱን ታዛቢዎች ይናገራሉ። የሪክ ማቻር ሃይሎች ሃይላቸውን...
View Articleየሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ንብረት በሆነው ኢትዮ ድሪም የአበባ እርሻ የሚሰሩ ሰራተኞች ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው ተናገሩ
ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በምዕራብ ሸዋ በሆለታ ገነት የሚገኘው የሼክ ሙሃመድ አላሙዲጅ ንብረት በሆነው ” ኢትዮ ድሪም” ድሪም የአበባ እርሻ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ላለፉት ሁለት ወራት ደሞዝ ያልተከፈላቸው በመሆኑ እነሱና ቤተሰቦቻቸው ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል። ሰራተኞች...
View Articleአንድነት ፓርቲ በእስር ላይ የሚገኙት አመራሮቹ ኢሰብአዊ ድርጊት እንደተፈጸመባቸው አስታወቀ
ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለአንድ ሳምንት ያክል በታሰረበት ክፍል ውስጥ እንዲጸዳዳ መደረጉን፣ ለ3 ቀናት በጨላ ክፍል ውስጥ ታስሮ የበቀል እርምጃ እንደተወሰደበት ፓርቲው በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ...
View Articleመንግስት በጸጥታ ዙሪያ የቴፒን ህዝብ ሰበሰበ
ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በርካታ ቁጥር ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት በቴፒ ከተማ በብዛት መታየታቸውን ተከትሎ መንግስት የከተማውን ህዝብ አርብ ጥቅምት 20፣ በትልቁ አዳራሽ በመሰብሰብ፣ በአካባቢው የሚታየውን ችግር በጋራ እንፍታ በማለት ጥሪ አቅርቧል። ለግማሽ ቀን በተካሄደው...
View Articleየቡርኪናፋሶ ወጣቶች ተቃውሞ ባነሱ ማግስት መሪያቸውን አባረሩ
ጥቅምት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለ27 አመታት አገሪቱን የመሩት ብሌስ ካምፓወሬ፣ እንደገና ለመመረጥ የነበራቸውን ፍላጎት ተቃውሞ መነሳቱን ተከትሎ መተዋቸውን ካስታወቁ በሁዋላ፣ የሽግግር መንግስት ፕሬዚዳንት በመሆን ለማገልገል መፈለጋቸውን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጅ ተቃዋሚዎች ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን...
View Articleበአዲስ አበባ ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ቤት ፈላጊዎች ቢኖሩም ችግሩን ለመፍታት የሚደረገው እንቅስቃሴ ደካማ ነው ተባለ
ጥቅምት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስአበባ የመኖሪያ ቤቶችን እጥረትን ለመፍታት ዳግም በተደረገው ምዝገባ ከ993 ሺ በላይ ቤት ፈላጊዎች መመዝገባቸውንና ይህን የቤት ፍላጎት ለማርካት በመንግስት በኩል እየተካሄዱ ያሉ ግንባታዎች አፈጻጸም ደካማ መሆኑን ከኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት...
View Articleታዋቂዎቹ የእንግሊዝ ጋዜጦች መንግስታቸው በኢትዮጵያ ላይ የሚከተለውን ፖሊሲ እየነቀፉ ነው
ጥቅምት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንግሊዝ አገር የሚታተሙ ጋዜጠኞች ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ በቂ ሽፋን አይሰጡም በሚል ሲተቹ ቢቆይም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በማንሳት እንግሊዝ በኢትዮጵያ የምትከተለውን ፖሊሲ የሚነቅፉ ዘገባዎችን እያወጡ ነው። ዘ ቴሌግራፍ ” እርዳታችን...
View Articleበምስራቅ የአገሪቱ ክፍል በርካታ የኢንተርኔት ቤቶች ተዘጉ
ጥቅምት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሃረርና የድሬዳዋ ወኪሎች እንደዘገቡት ከጥቅምት 17 ጀምሮ ከአዲስ አበባ የመጡ የፌደራል የጸረ ሽብር ግብረ ሃይል አባላት መሆናቸውን የገለጹ እንዲሁም የፌደራል ፖሊሶች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የኢንትርኔት ቤት ባለቤቶችን ይዘው በማሰር ወደ ማእከላዊ እስር ቤት...
View Articleመንግስት በ10 ፖለቲከኞችና ላይ ክስ መሰረተ
ጥቅምት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል አቃቢ ህግ በ10 ተከሳሾች ላይ የሽብርተኝነት ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው ሲሆን አብዛኞቹ ተከሳሾች ከግንቦት7 እና ከደሚት ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለዋል። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ሲሰየም ተከሳሾች...
View Articleግንቦት7 በጣሊያን ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር የተሳካ ስብሰባ ማካሄዱን ገለጸ
ጥቅምት ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጀቱ እሁድ እለት በሮም ባካሄደው ስበሰባ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተው ድርጅቱን ወክለው ከተገኙት ከአቶ አበበ ቦጋለ ጋር ውይይት አድርገዋል። የፖለቲካ ድርጅቶች በጣሊያን ስብሰባ ሲያደርጉ ባይታይም፣ ግንቦት7 ያካሄደው ስብሰባ ግን የተሳካ እንደነበር...
View Articleእንባጮ ተብሎ የሚጠራው አደገኛ መጤ አረም በጣና ሃይቅ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን የአካባቢው አርሶ አደሮችና...
ጥቅምት ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መጤ አረሙ ከሸፈነው መሬት ሁለት ሺህ ሄክታር በሩዝ ማሳ ላይ ሲሆን ቀሪው በኃይቁና በዙሪያው በሚገኙ ውሃ አዘል መሬት ላይ መሆኑን ተገልጿል፡፡ አረሙ በደንቢያ፣ በጎንደር ዙሪያ፣ በሊቦ ከምከም፣ በፎገራና በደራ ወረዳ በሚገኙ 16 ቀበሌዎች በፍጥነት እየተዛመተ...
View Articleለሁለት ወራት ደሞዝ ያልተከፈላቸው የኢትዮ-ድሪም ሰራተኞች የአንድ ወር ደመወዝ ተከፈላቸው
ጥቅምት ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሆለታ ገነት የሚገኘው የሼከ አላሙዲ ንብረት የሆነው “ኢትዮ ድሪም” የአበባ እና የእንጆሪ ሰራተኞች ጥቅምት 21 እና 22 ከፍያ ተፈጽሞላቸዋል። ሰራተኞች ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው ለኢሳት ባስተዋቁ በቀናት ውስጥ እንደተከፈላቸው ቢገልጹም፣ አሁንም ከሰራተኞች...
View Articleየመኢአድ አባላት እየታደኑ በመታሰር ላይ ናቸው
ጥቅምት ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መጪውን ምርጫ ተንተርሶ በሚመስል መልኩ በምስራቅና ምእራብ ጎጃም አመራሮችና አባላት መታሰራቸውን ድርጅቱ አስታወቀ በተመሳሳይ ዜና ደግሞ የወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ እና የዞኑ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወኖ በዳሳ ጥቅምት 22 ቀን 2007...
View Articleከፍተኛው ፍርድ ቤት በ16 የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ ውሳኔ አስተላለፈ
ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ፍርድ ቤቱ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ተይዘው በነበሩት ተማሪዎች ላይ ከ1 እስከ 5 በሚደርስ እስር እንዲቀጡ ውሳኔ አሳልፏል። በሌላ ዜና ደግሞ በአዳማ ቤታቸው የሚፈርስባቸው ሰዎች ባስነሱት ተቃውሞ ፖሊሶች ተጎዱ። የአከባቢው ነዋሪዎች...
View Articleበሰሜን ጎንደር ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ
ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቅማንት ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ በተጠራ የስራ ማቆም አድማ በዞኑ የሚገኙ ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ካለፈው አርብ ጀምሮ የተዘጉ ሲሆን፣ መንግስት እስከ መስከረም 30 መልስ የማይሰጥ ከሆነ፣ ተቃውሞው ግብር ባለመክፈል እንደሚቀጥል አስተባባሪዎቹ...
View Articleዘጠኝ ፓርቲዎች የሚሳተፉበት ትብብር የመጀመሪያ የትግል ስትራቴጂውን ይፋ አደረገ
ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ ትብብር የመሰረቱ 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አድርገዋል። ‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ...
View Articleበምእራብ አርማጭሆና በመተማ የአንድነት ፓርቲ አደራጆች ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ታፍነው ተወሰዱ
ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ የተላኩ የፌደራል ፖሊስ አባላትና ደህንነቶች፣ ወደ ፓርቲው መሪዎች ቤት ከንጋቱ አስራ አንድ ሰአት ላይ በመሄድ፣ መኖሪያ ቤቶቻቸውን ሰብረው በመግባትና አንዳንዶችንም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመደብደብ አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ ወስደዋቸዋል። የመተማ...
View Article