Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

የአንበጣ መንጋ በሰሜን ጎንደር አካባቢ መታየቱን ነዋሪዎች  ገለጹ

$
0
0

ግንቦት ፳፮(ሃያ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያን እየጎበኘ የሚመስለው የአንበጣ መንጋ በደብረ ብርሃን አካባቢ ከታየ በሁዋላ ትናንት እና ዛሬ ሰሜን ጎንደር አካባቢ ባሉ ወረዳዎች መታየቱን የአካባቢው ሰዎች ለኢሳት ገልጸዋል።

ወቅቱ የሰብል አዝመራ የሌለበት በመሆኑ አንበጣው ጉዳት አለማድረሱን ነዋሪዎች አክለው ገልጸዋል።

የአንበጣ መንጋው በአዲስ አበባም የተወሰኑ አካባቢዎች ታይቶ እንደነበር ይታወሳል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145