መንግስት በእስልምና ትምህርት ቤቶች ውስጥ ህገመንግስት ለማስተማር ሞክሮ እንደነበር ገለጸ
መጋቢት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት ለዲፕሎማቶች እና ለሚኒስትሮች በተሰጠው ስልጠና ላይ እንደተገለፀው እስላማዊው መጅሊስ እራሱን የመምራት አቅም አልነበረውም ተብሎአል፡፡ ቀድሞ የነበረው መጅሊስ ሰነፍ የነበረና የራሱን ትምህርት ቤት ለመምራት ብቃት ያለነበረው...
View Articleለገጠሩ ወጣት የምንሰጠው መሬት ባለመኖሩ እየተሰደደ ነው ሲሉ አቶ ሃለማርያም ተናገሩ
መጋቢት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ይህን ያሉት ኢህአዴግ የ6 ወራት የስራ አፈፃፀሙን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዳራሽ በገመገመበት ወቅት ነው። ስራ ፈጠራውም ሆነ ሳይታረሱ የኖሩትን ወል መሬቶችን እያደራጁ ለወጣቱ አርሶደአር መስጠት አላዋጣም ያሉት አቶ...
View Articleየኬንያ መንግስት በአገሪቱ የሚገኙ የሶማሊያ ስደተኞች ወደ ካምፖች እንዲገቡ አዘዘ
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኬንያ ይህን ህግ ያወጣችው የሶማሊያ ስደተኖች የጸጥታ ችግር ፈጥረውብኛል በሚል ነው። ሁሉም የሶማሊያ ስደተኞች ካኩማ እና ደደሃብ ወደሚባሉት የስደተኞች ካምፖች እንዲገቡ ይህን ባማያደረጉ ስደተኞች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ መንግስት ገልጿል። አለማቀፍ ተቋማት...
View Articleበሶማሊ ክልል ከ400 ሺ ዶላር በላይ ገንዘብ በህገወጥ መንገድ ከአገር ሲወጣ ተያዘ
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የደረሰው ዜና እንደሚያመለክተው ባለፈው ሳምንት ውጫሌ በሚባለው የጠረፍ ከተማ ላይ ከ400 ሺ ዶላር በላይ ገንዘብ በአይሲዙ መኪና ተጭኖ በህገወጥ መንገድ ሲወጣ በፌደራል ፖሊሶች ተይዟል። ሾፌሩና እና አብረው የነበሩ ሰዎች መጥፋታቸው ሲታወቅ ሁለት...
View Articleየሃረሪ ሬዲዮ የኦሮምኛ ፕሮግራም አዘጋጅ ታሰረ
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ ጀማል ዳውድ ካለፉት 8 ቀናት ጀምሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ የታወቀ ሲሆን፣ ለእስር የዳረገውም መልእክቶችን በሞባይል ስልክ ልኸሃል ተብሎ ነው። ይሁን እንጅ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ሰዎች እንደገለጹት ጋዜጠኛ ጀማል የታሰረው በክልሉ ውስጥ የሚታየውን...
View Articleየጨፌ ኦሮምያ የክልሉን መሪ ይመርጣል ተብሎ እየተጠበቀ ነው
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ሲጀመር ባለፉት ተከታታይ ቀናት ለውይይት ቀርቦ የነበረውን ሪፖርት ያለምንም ተቃውሞ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ምክር ቤቱ በሞት የተለዩትን የቀድሞውን ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳን ለመተካት አዲስ ፕሬዚዳንት የሚመርጥ ሲሆን፣...
View Articleበሻኪሶ ከ200 በላይ የኦሮሞ ተወላጆች ታስረዋል ሲል አፍሪካ ቀንድ የሰብአዊ ሊግ አስታወቀ
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአፍሪካ ቀንድ የሰብአዊ መብት ሊግ ባወጣው መግለጫ በደቡብ ኦሮምያ በጉጂ ዞን በሻኪሶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚማሩ ቁጥራቸው 200 የሚጠጋ ተማሪዎች በአዶላ ከተማ መታሰራቸውን ገልጿል። ብዙዎቹ ወጣቶች ከጸጥታ ሃይሎች በተተኮሰ ጥይት እና ድብደባ...
View Articleበመርዓዊ ከተማ በመቶዎች የሚቆጠሩ ህጻናትና አርሶደአሮች ታሰሩ
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ ጎጃም ዞን በሜጫ ወረዳ በእናሸንፋለን ቀበሌ በጨቦች ጎጥ ለአበባ ምርት በሚል የከርሰ ምድር ውሃ ለማውጣት መንግስት እንቅስቃሴ መጀመሩን የተቃወሙ ቁጥራቸው ከ200 እስከ 300 የሚደርስ አርሶ አደሮች፣ እድማያቸው ከ9 እስካ 12 የሚደርስ ታዳጊዎች፣...
View Articleየብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ዳግም ቃጠሎ
መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በማተሚያ ቤቱ የወረቀት ክምችት መጋዘን ላይ መጋቢት 13 ቀን 2006 ዓ.ም ከሰዓት በሃላ በተነሳ ድንገተኛ የእሳት አደጋ መጋዘኑን የጎዳ ሲሆን ትናንት ጠዋት ደግሞ በዚሁ መጋዘን ላይ ተመሳሳይ አደጋ አጋጥሞአል፡፡ የመጀመሪያው አደጋ በማተሚያ ቤቱ የወረቀት...
View Articleየሙስሊም ኢትዮጵያውያን ቀጣይ የተቃውሞ መርሃግብር
መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት 2 አመታት ሲካሄድ የቆየው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጋብ ብሎ የነበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አርብ እንደሚጀመር ታውቋል። የተቃውሞ መሪ መፈክሩ “ሰላታችንን በመስኪዳችን” የሚል እንደሆነና መስኪዶችን በመንግስት ታማኞች ለማስያዝ የሚደረገውን...
View Articleየጫፌ ኦሮምያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ
መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጨፌ ኦሮምያ ትናንት የጀመረውን የምክር ቤቱን መደበኛ ስብሰባ ሲያጠናቀቅ ምክትል ጠ/ሚኒስትር እና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒሰትር የሆኑትን አቶ ሙክታር ከድርን በፕሬዚዳንትነት፣ እንዲሁም አቶ ለማ መገርሳን በአፈ ጉባኤነት መርጧል። ምንም አይነት ተወዳዳሪ እጩ...
View Articleበኦሮምያ ክልል በጉጂ ዞን የተፈጠረው ግጭት
መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መጋቢት 16፣ 2006 ዓም ከጉጂ ዞን ዋና ከተማ ስያሜ ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ግጭት ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎች እንደሞቱ የአካባቢው ሰዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ግጭቱ የጉጅ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ነገሌ ቦረና ፣ ነገሌ ብቻ ተብላ እንድትጠራ...
View Articleወንድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ የፀጉር አቆራረጥ ስታይላቸውን እንደ ሀገሪቱ ፕሬዚዳንት እንዲያደርጉ ሰሜን ኮሪያ መመሪያ...
መጋቢት ፲፰ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ራዲዮ ፍሪ ኤሺያን በመጥቀስ ቢቢሲ እንደዘገበው፣መመሪያው መጀመሪያ የተላለፈው በዋና ከተማዋ በፒዮንግያንግ ከሁለት ሳምንት በፊት ነው። በአሁኑ ወቅት በ ሀገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሙሉ አዋጁ ተግባራዊ እየሆነ መምጣቱን የዜና አውታሩ ጠቁሟል። በወጣት...
View Articleበመርአዊ ከተማ ተጨማሪ አርሶደአሮች እየታሰሩ ነው
መጋቢት ፲፰ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ ጎጃም ዞን በሜጫ ወረዳ በእናሸንፋለን ቀበሌ ከአበባ እርሻና ከውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት የሚታሰሩ አርሶደሮች ቁጥር መጨመሩን አካባቢው ሰዎች ገልጸዋል። በወረዳው ዋና ከተማ በመርአዊ ከተማ አሁንም የሚታሰሩ አርሶደአሮች መኖራቸውን...
View Articleሙስሊም ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ አሰሙ
መጋቢት ፲፰ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት ሁለት አመታት ሲካሄድ የቆየው፣ ከቅርብ ወራት ወዲህ ቀዝቀዝ ብሎ የነበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ዛሬ ቁጥሩ እጅግ ብዙ የሆነ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በአንዋር መስጊድ ተካሂዷል። ሙስሊም ኢትዮጵያዊያኑ አላህ ሰላምን እንዲያመጣ...
View Articleበጉጂ እና በቦረና ተወላጆች መካከል በተፈጠረ ግጭት የማቾች ቁጥር መጨመሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ
መጋቢት ፲፰ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ያነጋገራቸው የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት ባለፉት 3 ቀናት ከቦረና እና ከጉጂ ጎሳዎች ከ20 ያላነሱ ሰዎች ሲሞቱ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። ብዙ ቤቶች መቃጠላቸውንና መጠኑ በውል ያልታወቀ ንብረት መውደሙንም ነዋሪዎች ይገልጻሉ። በተለይ...
View Articleበናይጀሪያ መከላከያ ሰራዊቱ ከ600 በላይ ሰዎችን መግደሉን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ
መጋቢት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታዋቂው የሰብኢ መብቶች ተከራካሪ ድርጅት አምነስቲ እንደገለጸው የናይጀሪያ መከላከያ ሰራዊት፣ የእስልምና መንግስት ለማቋቋም የሚታገለውን ቦኮ ሃራም የተባለውን ተዋጊ ሃይል ለመውጋት በሚል ሰበብ በከፈተው ጥቃት ከ600 በላይ ዜጎች ተገድለዋል። መከላከያ ሰራዊቱ...
View Articleየኩረጃ መስፋፋት የትምህርት ጥራትን እየጎዳ ነው ተባለ
መጋቢት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብሔራዊ ፈተናዎች በተለይ የ8ኛ እና የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናዎች ላይ ኩረጃ በአሳሳቢ ደረጃ እየተባባሰ መምጣቱን፣ ለትምህርት ጥራት ማሽቆልቆል አንድ ምክንያት እየሆነ መሆኑን የፌዴራል የስነምግባርና ጸረ ሙስና ኮምሽን ያካሄደው ጥናት ጠቁሟል፡፡ ሰሞኑን...
View Articleበሀረር ከተማ በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ ድበደባ እየተካሄደባቸው ነው
መጋቢት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የእስር ቤት ምንጮች እንደገለጹት በሀረር ከደረሰው ተደጋጋሚ ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ተቃውሞቸውን አሰምተዋል በሚል የታሰሩት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በፌደራል ደህንነት መርማሪዎች ከፍተኛ ድብደባ እየተካሄደባቸው ነው:፡ ፖሊስ ጋራጅ ውስጥ የታሰሩት ወጣቶች ከምግብ...
View Articleበጉጂና በቦረና መካከል የተፈጠረውን ግጭት የአገር ሽማግሌዎች ጣልቃ ገብተው ማብረዳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ
መጋቢት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ20 በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ሞት ምክንያት የሆነውን በጉጂ ዞን የተከሰተውን የጎሳ ግጭት ለማስቆም የኦሮሞ የአገር ሽማግሌዎች ወደ አካባቢው ተንቀሳቀስው የሁለቱን ጎሳዎች ሰዎች ካነጋገሩ በሁዋላ ላለፉት 4 ቀናት የተካሄደው ግችት ሊቆም ችሎአል። ምንም እንኳ...
View Article