Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

የመለስ ፋውንዴሽን የገንዘብ ስብሰባ ህዝቡ እንዳይቆጣ በሚል ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ተደረገ

$
0
0

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመለስ ዜናዊን ፋውንዴሽን እንሰራለን በሚል ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችና አርሶአደሮች በነፍስ ወከፍ ከ50 ጀምሮ

እንዲያዋጡ መገደዳቸው በቅርቡ ከተደረገው የደሞዝ ጭማሪ ጋር ተያይዞ የህዝቡን ቁጣ ሊያባብሰው ይችላል ተብሎ በመሰጋቱ ፣ የገንዘብ መሰብሰቡ ሂደት ለጊዜው እንዲቋረጥ

መደረጉን የኢህአዴግ ምንጮች ገልጸዋል።

ፋውንዴሽኑን ለማሰራት ከሚፈለገው ገንዘብ 10 እጥፍ እንደተሰበሰበ የሚነገርለት ፋውንዴሽን በወ/ሮ አዜብ መስፍን የሚመራ ሲሆን እስካሁን ድረስ ወጪና ገቢውን በተመለከተ

ለህዝብ ለማሳወቅ ባለመድፈሩ ከድርጅቱ አባሎች ትችቶች እየቀረቡበት ነው።

በአዲስአበባነዋሪዎችዘንድከፍተኛምሬትያስከተለውይህየገቢማሰባሰቢያበለፉትሁለትሳምንትበድርጅቱደጋፊዎችአማካኝነትየገንዘብማሰባሰቢያደረሰኝበመያዝበከተማውሁሉምቀበሌዎችና

በአንዳንድየወረዳየመንግስትመ/ቤቶችሲዘዋወሩየታየቢሆንም፣  በዚህሰሞንደግሞበደመወዝጭማሪውቅርየተሰኘውህዝብብሶትላለማባባስበሚልለጊዜውዘመቻውእንዲረግብተደርጓል፡፡

ዘመቻው የህዝቡ ምሬት “ቀንሷል” ተብሎ ሲታመን ሊቀጥል እንደሚችል መንጮች አክለው ገልጸዋል።

በቅርቡ የተደረገው የደሞዝ ጭማሪ የኑሮ ውድነቱን እያባባሰው መሆኑን በእየለቱ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

Trending Articles