Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

ኢህአግ በሁመራ አካባቢ ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ

$
0
0

ግንቦት ፳፯ (ሀያ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በሉግዲና በበረከት ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።

በግንቦት 25-2005 ዓ.ም በሁመራ ልዩ ስሙ በረከት በተሰኘ ስፍራ ከመከላከያ ሰራዊት  35ኛ ክፍለጦር እና ከሚሊሻ ሰራዊት ጋር በተከታታይ በስምንት/8/ ዙር ፋታ የለሽና እልህ አስጨራሽ ውጊያ 148 ሙት፣ 374 ቁስለኛ፣ 31 ክላሽንኮፍ ጠመንጃ፣  47 የእጅ ቦንብ ፣2 ስናይፐር፣ 3 መትረየስና የተለያዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን መማረኩን አስታውቋል።

በግንቦት 24 እና  25-2005 ዓ.ም በተካሄደው ውጊያ ደግሞ በድምሩ 192 ሙት፣  440 ቁስለኛ ቁጥራቸው የበዛ ተተኳሽ መሳሪያዎችን ከነትጥቃቸው መማረክ መቻሉን ገልጿል። ኢሳት የመንግስትን አስተያየት ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም አልተሳካለትም።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

Trending Articles