Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

ኔልሰን ማንዴላ 95 አምስተኛ ልደታቸውን አከበሩ

$
0
0

ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የደቡብ አፍሪካው የነጻነት አባትና የመጀመሪያው ጥቁሩ ፕሬዚዳንት ኔልሰን ማንዴላ 95 ኛ አመት የልደት በአላቸውን በሆስፒታል አልጋቸው ላይ ሆነው አክብረዋል።

ማንዴላን እንኳን አደረሰዎት ለማለት በሆስፒታሉ የተገኙት የወቅቱ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የማንዴላ ጤና መሻሻል እንዳስደሰታቸው ታናግረዋል። ” እንኳን አደረሰህ” ስላቸው በፈገግታ መልሰውልኛል ብለዋል ጃኮብ ዙማ።

የአገሪቱ ነዋሪዎች የማንዴላን የ67 አመታት የፖለቲካ ህይወት ለመዘከር የ67 ደቂቃ የነጻ አገልግሎት ስራ በመስራት አስበዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

Trending Articles