Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

በአዲስ አበባ የአንድነት ፓርቲ አባሎች እየታሰሩ ነው

$
0
0

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-ፓርቲው በደሴና እና በጎንደር የተሳኩ የተቃውሞ ሰልፎችን ባካሄደ ማግስት ከ30 በላይ አባሎቹ በዋና ከተማዋ የተቃውሞ ፊርማ ሲያሰባስቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

ባለፉት ሳምንታትትም በተመሳሳይ መንገድ የታሰሩ እና የፍርድ ቤት ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ያሉ አባላት አሉ።

አንድነት ፓርቲ ለ3 ወራት በሚቆየው የተቃውሞ እንቅስቃሴ  በዋና ዋና ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን ከማካሄድ ባሻገር ቤት ውስጥ ስብሰባዎችንና እና 1 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ፊርማ ያሰባስባል።

ፓርቲው በደሴና በጎንደር ያደረገው ተቃውሞ ለፓርቲው አባላት ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠረ አንዳንድ አባላቱ ተናግረዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

Trending Articles