Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ባለፉት ሁለት ዓመታት በእጅጉ ማሽቆልቆሉን >የተሰኘ ተቋም ይፋ አደረገ።

$
0
0

ጥር ፲፪(አስራ ሁለት ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ልጅ በሆኑት  በዶክተር አሉላ ፓንክረስ የሚመራው  <፣ያንግ ላይቭስ>> ሰሞኑን ይፋ ባደረገው ጥናት  ኢትዮጵያ ውስጥ  የትምህርት ደረጃና ጥራት ከክልል-ክልል እንደሚለያይ ጠቁሟል።

ትምህርት ከጀመሩ ተማሪዎች መካከል  17 በመቶ ያህሉ በተለያዩ  ችግሮች እንደሚያቆሙ  ያመለከተው ጥናቱ፤ ከሚማሩት መካከልም 24 በመቶዎቹ  ወደተከታዩ ክፍል ማለፍ እየተሳናቸው እንደሚደግሙ  ይጠቁማል።

ዋና ጽህፈት ቤቱ በእንግሊዝ የሆነው<< ያንግ ላይቭስ>> የኢትዮጵያን  የትምህርት ጥራት አሰመልክቶ ያጠናውን  ይህን ጥናት ሰሞኑን  በአዲስ አበባ  ይፋ አድርጓል።

ባለፉት አመታት በኢትዮጵያ  የትምህርት ጥራት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቀለ  እንደመጣ  በርካታ  ምሁራን  በተደጋጋሚ ሲናገሩ ቆይተዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

Trending Articles