Quantcast
Channel: Amharic
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

የእስቴ መምህራን ተቃውሞ አሰሙ

$
0
0

ታኀሳስ ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :- በደቡብ ጎንደር እስቴ ወረዳ የሚገኙ  መምህራን ለ3 ቀናት የሚቆይ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ስብሰባ እንዲካፈሉ ቢጠሩም፣ መምህራኑ በስብሰባው ላይ ከተገኙ በሁዋላ፣ በአንድ ድምጽ ስብሰባ ኣንሳተፍም በማለት ጥለው ወጥተዋል። መምህራኑ መንገድ የመሳሰሉ የመሰረተ-ልማቶች አልተሟሉም፣ ለመምህራን በቂ የሆነ ክፍያ አይሰጥም በማለት ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።

በዚህ ሁኔታ ውስጥ የተጠራው ስብሰባ በተቃውሞ ታጅቦ መበተኑንና የመምህራኑ  ያለተጠበቀ እርምጃ የአካባቢውን ባለስልጣናት ማስደንገጡን መምህራን ለኢሳት ገልጸዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2145

Trending Articles